የጉዞ ነገር…

images.jpgሁሉም የአፍሪካ አገራት ነዋሪዎች ወደኢትዮጵያ ለመግባት፣ በደረሱ ጊዜ ቪዛ ማግኘት የሚችሉበት አሠራር፣ ከኖቬምበር 10 ይጀምራል ተብሎ ነበር። (እንዴት ሆነ እንኳን “እንኳንስ ዘንቦብሽ እንዲሁም ጤዛ ነሽ” ይላሉ። የደህንነት ሁኔታው እንዲህ በሆነበት ጊዜ ጣጣው ብዙ ነው።
 
እሱን ባሉ በ20 ስንተኛ ቀኑ፥ አሁን ደግሞ ፓስፖርት ለማውጣት ቁም ስቅል ሆኗል ተብሏል። ወዳጆች ነገሩን ሲያወሩት ይኽን ያህል የተጋነነ ችግር አልመሰለኝም ነበር። ሰው እንዴት ፓስፖርት ለማውጣት መከራውን ያያል?
 
የሚሄድበት አገር ይጭነቀው እንጂ፣ እንዴት እና በምን ተለይቶ ይስተናገዳል?
 
ማን ነው አንቺ ቱሪስት ትመስያለሽ፣ አንቺ አትመስዪም ማለት የሚችለው?
 
በምንስ መስፈርት ነው?
 
ለምንስ እንደዚያ ይደረጋል?
 
በር ዘግቶ ስደት አስቀርተናል ለሚል ሪፖርት ነው?
 
ማንኛውም ሰው ከቦታ ቦታ የመንቀሳቀስ መብት አለው።
የሚሄድበት አገር አልቀበል ካላለው በስተቀርም፣ የፈለገበት ቦታ ሄዶ የመስራት እና የመኖር መብት አለው።
 
መብት የሆነውን ነፍገው፥ ምን ሸፍጥ እንዳሰቡ እንጃ… በጎን ለጎዳና ተዳዳሪዎች እና ለረጅም ጊዜ አዲስ አበባ ውስጥ ለኖሩ ሰዎች ጊዜያዊ መታወቂያ እንሰጣለን ይላሉ። ለምን አስፈለገ?
 
በዚህ በግርግር የቀበሌ ቤቶች ከድሃ ተነጥቀው ለባለጊዜ እየተሰጡ ነው ተብሎ በሚወራበት እና ምርጫና፣ ሕዝብ እና ቤት ቆጠራ በደረሰበት ጊዜ መታወቂያ መስጠቱ ለምን አስፈለገ?
 
መታወቂያው ቀርቶ ፓስፖርት ይሰጣቸውና እንደኢዮጵያዊ ይቆጠሩ።
 
#የጉድአገር

ስለሀሳብ ልዕልና ሲወራ…

ምርጫውን ፍትሀዊ እና ዴሞክራሲያዊ ለማድረግ የተደረገው የቃል ተስፋ መልካም ነው። እግዚግዚአብሔር ፈቅዶ ምርጫው ነጻ ሆኖ ቢከናወን ግን፣ ኢህአዴግ በምን ቁመናው ሊቀጥል ይችላል? 🤔
 
በርግጥ “ከማያውቁት መልዐክ የሚያውቁት ሰይጣን” በሚል ብሂል የሚገብርላቸው ሊኖር ቢችልም ቅሉ፥ ለክፋታቸው ሲነዙት የኖሩት የብሄር አጀንዳ መልሶ እነሱኑ ሳይሰለቅጥ የሚመለስ በማይመስል መልኩ ተቀጣጥሏልና፥
 
“ምርጫው በነጻ እና ፍትሀዊ መንገድ እንዲደረግ ፈቃደኞች/ቁርጠኞች ነን” ማለታቸውን በራሱ፣ በሰላም እንደሚለቁ ቃል የገቡ ያህል እቆጥረዋለሁ።
 
(የሚነደው ግን፥ የነጻ እና ፍትሀዊ ምርጫ ወሬ እና ምኞት እንኳን ካለነሱ ፈቃድ የማይቻል የነበረ መሆኑ ነው። ይኽንንም ውለታ እንደዋሉ እንጂ መሆን እንዳለበት አይቆጥሩትም።)
 
ኢህአዴግ “ሀሳብ ሸጠን ነው የምናሸንፈው” ሲልና ስለሀሳብ ልዕልና ሲያወራ መስማት ይገርማል። እንደው ምናልባት በታምራት ደስታ (ነፍስ ይማር)
 
አንድ ዕድል ሰጥተሽኝ ልካስሽ ደግሜ፣
ያውም አገልጋይሽ ታማኝ ባሪያሽ ሆኜ
“አንድ ዕድል ሰጥተሽኝ ልካስሽ ደግሜ፣
ያውም አገልጋይሽ ታማኝ ባሪያሽ ሆኜ”
 
ብለው ይጀነጅኑን እንደው እንጂ ምን ቀራቸው?
 
አብረው ተባብረው ዘረፉ፣ ገረፉ፣ ደፈሩ፣ አባረሩ፣ ጣት ቀሰሩ፣ ጣት እንቆርጣለን ብለው ፎከሩ፣ ከፋፍለው አባሉ፣ ቀለም ጠልተው ቀለም ደፍተው፣ የቀለም ቀንድ ሰባብረው፣ ሕዝቡን በድንቁርና አጥረው አኖሩት፣ (ከርሞ ማመናቸውም ተመስገን ነው)፣ ምኑ ቅጡ ተሰፍሮ ተዘርዝሮ ያልቅና?
 
በተጭበረበረ ምርጫ ገነው፣ አሁንም በየመሀሉ በሊቀመንበራቸው በኩል “ተፎካካሪ” ያሉትን ይወቅሳሉ። ያስጠነቅቃሉ። ላይ ላዩን ገር ሆነው፣ ውስጥ ውስጡን አሁንም በሚዛን ሲቀመጡ እነሱ እንደሚሻሉ ያስባሉ። ያሳስባሉ።
 
በምርጫ ምክንያት ለተፈጠሩ ቀውሶች በሙሉ ዋናው ድርሻ ኢህአዴግ እንጂ ማን ሆኖ፣ አሁን “ወደኋላ ሄዶ ያለፈውን ማንሳት እና በትናንት መኖር አያስፈልግም” ካሉ በኋላ፣ በጨው መታጠብ ካልሆነ በቀር፣ መለስ ቀለስ እያሉ ሌላውን ለመውቀስ እና አበክሮ ለመውቀስስ ምን አቅም ያገኛሉ?
 
የኢህአዴግ ነገርማ
ያልጠፋነው፣
ከእግዚአብሔር ምህረት የተንሳ ነው”ን
እያስዘመረን የሚኖር ጉዳይ ነው!
 
እግዜር ቸር ቸሩን ያድርግልንማ!

ኢህአዴግ ጋዝ የነካው ምግብ…

ኢህአዴግ ጋዝ የነካው ምግብ ነው ስንል በምክንያት ነው። የጥቅም እና ዝርፊያ ተካፋይነቱን ሕወሃት የበላይ ሆኖ ቢሰፍርበትም፥ ትናንት ሁሉም በተመቸው እና ጊዜው በፈቀደለት ልክ ዘግኗል፣ አንገላቷል፣ በየፈርጁ እና በየደረጃውም፥ የግፉም የዝርፊያውም ተካፋይ ነበር። የሚደርሰው ወንጀል እና የሰብዓዊ መብት ጥሰት ሁሉ እንዳይታወቅ በመሸፋፈን ረገድም ሁሉም አባል ይኽ ነው የማይባል ሚና ተጫውቷል። ምንም እንኳን በሕወሃት የበላይነት ቢዘወርም፥ የሰብአዊ መብት ጥሰቱን እና ንጹሐንን የማፈኑን ሥራም በድርጅት ደረጃ አቋም እና አተገባበር ይዘው ሲያደርጉት የነበረው ነውና፣ የጭንቀት ቀን ሲመጣ ጣት መቀሳሰሩ በኅሊና ዳኝነት ፊት የትም አያደርስም። ማናቸውም አሸባሪውን ድርጅት ሲያገለግሉ እንጂ፣ ገዳም አልነበሩም።

ሁሉም ደርሶ በድል አጥቢያ አርበኝነት ስሜት እና በለውጠኝነት ሽፋን ጣት ቀሳሪ ይሁን እንጂ፣ ለመዛኝ እና ለፈራጅነት የሚያበቃ ንጽህና ያለው ያን ያህል አይደለም። ምንም አያውቅም የሚባለው አባል እንኳን፣ ቢያንስ ዝም በማለት እና ንጹሐን ሲንገላቱ ባለመከላከል፣ ድሀ ሕዝብ ሲመዘበር የምዝበራው አበል ተካፋይ በመሆን እያመሰገነ እና፤ አባል ያልሆኑና ያገባኛል ያሉ ሰዎችን በጠላትነት እየፈረጀ ኖሯል። የኢትዮጵያ አምላክ ራቁት እሲያስቀር፣ የጊዜ ፈረስ እንዲህ በአፍጢም እስኪፈጠፍጥ ድረስ!

በርግጥ፥ አንድም ይሁን ሁለት፣ ያጠፋ ሰው መጠየቅ መጀመሩ አግባብ ነው። ሆኖም ግን፥ የሌላው ነውረኝነት አለመጋለጥ፣ የተጋለጡትን እና በህግ ለመጠየቅ መንገድ የተጀመረላቸውን ሰዎች ጉዳይ ስህተት አያደርገውም። ዛሬ ጊዜው ፈቅዷል፣ ትናንት አልፏል በሚል ቀመር፥ አብረው ሲፈተፍቱ፣ የሕዝብ ደም ሲገብሩ እና ነውሩን ሲጋርዱለት፣ በታማኝነት እና ቁርጠኝነት ሲያገለግሉት የነበሩትን ድርጅት “እኔ ከደሙ ንጹህ ነኝ” በሚል ጲላጦሳዊ ግብዝነት ሲነዛ ግን፥ አሁንም ህሊና ካለ ይፈርዳል።

እንደማሳያ፥ ሰሞኑን በድፍረታቸው እና አጋላጭነታቸው ተደንቀን፣ አፋችንን ከፍተን ሀቀኝነታቸውን የመሰከርንላቸውን አምባሳደር ሱለይማን ደደፎን የትዊተር ገጽ በጊዜ ወደ ኋላ ተመልሰን በመቃኘት ነገሬን ልቀጥል።

አቶ ሱለይማን ዛሬ ፓርቲአቸው ኦህዴድ የበላይ ባይሆን እና ሕወሃት ቢቀጥል ኖሮ፣ ሰጥ ለጥ ብለው የሚገዙ እንጂ “ግፍ አንገፈገፈኝ” ብለው የሚለቁ አይነት ነበሩ የሚያስችል የጀርባ ታሪክ እንዳላቸው የሚያሳይ ማስረጃ የለም። በርግጥ እሳቸው ብቻ ሳይሆኑ፣ ሌሎች አባላቶችም እንዲሁ ከመጣው ጋር ቀጥለው፣ በጥሎ ማለፍ ድርጅታቸውን እያሽሞነሞኑ ይቀጥሉ እንደነበር መገመትም ከባድ አይደለም። ድርጅታቸው ኢህአዴግን በታማኝነት ከማገልገል ባለፈ፥ ሲያደርግ የኖረውን ነገር በመሸፋፈን እና ተቃዋሚ ፓርቲዎችን በማሳጣት የተጫወቱት ሚና ብዙ ነው።

በኦክቶበር 2013 የአፍሪካ አገራት በኢትዮጵያ መንግስት አዘጋጅነት፣ እነ ኡሁሩ ኬኒያታ የሰው ልጆች ላይ ወንጀል በመፈጸማቸው  በሚል መከሰሳቸውን ለመከላከል፥ በአዲስ አበባ አስቸኳይ ስብሰባ አድርገው ነበር። አጀንዳቸውም የዓለማቀፉን የወንጀል ፍርድቤት International Criminal Court (ICC) ለመቃወም ነበር። ጠቅላይ ሚኒስትር የነበሩት አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ በተባበሩት መንግስታት ስብሰባ ተገኝተውም ፍርድቤቱን መተቸታቸውን ተከትሎ፥ የአፍሪካ መሪዎችን ስብሰባ ጠርተው ነበር። ነገሩ “ነግ በእኔ”፤ “አፍንጫ ሲመታ አይን ያለቅሳል” ነበር። በተለይ ደግሞ የነገሩ ጠንሳሽ ኢትዮጵያ መሆኗ “ፈስ ያለበት ዝላይ አይችልም” ዓይነት ነበር።

ታዲያ ያንን ተከትሎ፥ ከሁለት ወይም ከሶስት ሳምንታት በኋላ በኦክቶበር 28 ቀን፥ አቶ ሱለይማን

I am skeptical on the very intention to create the ICC. Why doesn’t it open its eyes on the whole globe than giving excess attention to Africa?

በማለት ለአምባገነኖቹ የአፍሪካ መሪዎች መቆርቆራቸውን ገልጸው ነበር።

1

ኖቬምበር 15 ቀን 2013፥ የሳውዲ አረቢያ መንግስት በኢትዮጵያውያን ላይ እየደረሰ የነበረውን ስቃይ እና የሰብዓዊ መብት ጥሰት በማውገዝ፣ ሰማያዊ ፓርቲ በሳውዲ አረቢያ ኤምባሲ ደጃፍ ላይ ለማካሄድ በጠራው የሰላማዊ ሰልፍ ላይ የወጡ ሰዎች፣ ላይ ፖሊስ የተቃውሞ ሰልፉን በመከልከል ሰዎችን ደብድቦ እና አስሮ ነበር።  ታዲያ በዚያን ቀን፥ አቶ ሱለይማን

Ethiopian Gov’t has allocated 50 million Birr to integrate Ethiopians deported from Saudi Arabia. But what do the opposition parties are doing? Ethiopian opposition parties are trying to benefit out of tears of Ethiopian migrants in Saudi Arabia as usual. Why?

ብለው በሁለት ትዊት ጽፈው ነበር።

2.jpg

በመጀመሪያ የኢትዮጵያ መንግስት ገንዘቡን የመደበው ከኢትዮጵያ ሕዝብ ንብረት ላይ መሆኑን ዘንግተውት እንደልግስና ቆጥረውት ተመጻድቀው ነበር። ገንዘቡ በአግባቡ ይዋል አይዋልም አይታወቅም። ሆኖም ግን፥ በወቅቱ ለወገን በመቆርቆር የተጠራን ሰልፍ ተከትሎ፣ የተቃዋሚ ፓርቲዎችን በጅምላ ለመፈረጅ እና፣ እንደ ኢህአዴግ አባልነታቸው “ተቃዋሚዎች በሕዝብ እንባ ለማትረፍ የሚሞክሩ ናቸው” ብሎ ስም ለመለጠፍ እና፣ “መንግስት ይህን ሲያደርግ፣ እነሱ ግን ምንም እንዳላደረጉ” ለማጉላት ዳክረው እንደነበር እናያለን።

20131115163925420734_20

(እንደፓርቲ ከአባላት ከሚያገኙት መዋጮ ላይ መቋቋሚያ እንዲሰጡ ጠብቀው ነበር ማለት ነው። እንደተቃዋሚ ፓርቲነታቸውም ለዜጎች ጥቃት መቆርቆራቸውንም አቃለዋል።) ከዚህ በላይ ኢህአዴን መጋረድ እና የሰብአዊ መብት ጥሰቱን መደገፍ ከየት ይመጣል?

እነ ወ/ሮ ሚሚ ስብሀቱ፣ አቤል ተስፋዬ እና መርከብ ነጋሽ ተሳትፈውበት በነበረ “የቀለም አብዮት” ዶክመንተሪ ማግስት፥ የዞን 9 ስድስት ጦማርያን እና 3 ጋዜጠኞች ወዳጆቻችን በአፕሪል 2014 መታሰራቸውን ተከትሎ፥ አቶ ሱለይማን፣ በሜይ 1 2014፥

Zone Niners are messangers of color revolution hired by neo-liberal masters. They are instructed to create violence ahead of next election. Press Freedom is not systematic invasion or campaign to change regime by color revolution. That is what the west are trying in Ethiopia.

ብለው ንጹሀን ላይ ጣታቸውን ቀስረው፣ እና የመንግስትን ጭቆና ለመሸፈን ሞክረው እንደነበርም እናስታውሳለን።

4.jpg

የመንግስትን የተጋነኑ “የኢንቨስትመንት” ወጪዎችን በተመለከተም፥ በዲሴምበር 3፣ 2014

Where will huge state investments lead Ethiopia? Obviously to growth

ብለው ጽፈው ነበር።

6

እንግዲህ ወደ እድገት ያመራናል ያሏቸውን ወጪዎች በተመለከተ ነው፣ አሁን ያላየ፣ ያልሰማ ሆነው በጻድቅ ምስክርነት የቆሙት። ምስክርነት መቆማቸውን መንቀፌ አይደለም፣ ነገር ግን ትህትና የቀላቀለ ቢሆንና፣ ሁላቸውም መነካካታቸውን የማይክድ መንፈስ ያረበበት አነጋገር ቢሆን የሚል የከሸፈ ጉጉት እንጂ።

በሌላ ማሳያ፥ የአሁኑ የጠቅላይ አቃቤ ህግ፣ የያኔው የፍትህ ሚንስትሩ አቶ ብርሃኑ ፀጋዬ፥ በ2011

ያለ ፍርድቤት ትዕዛዝ አይታሰርም። ያለፍርድቤት ውሳኔ አይቀጣም። በምርመራ ወቅት ድብደባ የለም። ግርፋት የለም። ሕገመንግስታችን ይከለክላል። እነዚህን ነገሮች ማለት ነው። ስለዚህ እንደዚህ ተደርጓል፣ እንደዚህ ተደርጓል ተብሎ አሉባልታ ካልሆነ በስተቀር በተጨባጭ እንደዚህ አይደረግም። በማረሚያ ቤት የሚገኙ፣ በምርመራ ላይ የሚገኙ፣ በፍርድቤትም የሚገኙ ማየትም፣ መጎብኘትም ይቻላል። እየተደረገም ነው። በውስጥም በውጭም ባሉት አካላት ነው። በዋናነት ለነዚህ አካላት አይደለም መንግስት እነዚህን ስራ የሚሰራው።

በዋናነት፥ ቅድም እንዳልኩት፣ ህገመንግስቱ ላይ የተቀመጡትን መብቶች የማስከበር፣ የማክበር ኃላፊነት የመንግስት ነው። ይሄም ህግ የወጣው፣ [የዜጎችን] መንግስት ሌት ተቀን እየሰራ ያለው፣ የዜጎችን መብትና ጥቅም ለማስከበር ነው እንጂ ሌሎች ሶስተኛ ወገን የውጭ አካላትን ለማስደሰት፣ ወይ ደሞ ለማስቀየም አይደለም። ለዜጎች፣ የዜጎችን መብት ለማስጠበቅ፣ በአገራችን ውስጥ የዴሞክራሲ ስርዓት ስር እንዲሰድ ለማድረግ ነው እየተሰራ ያለው እንጂ፤ ለነዛ አካላት ተብሎ የሚሰራ ነገር አይደለምና፣ ጣልቃ የሚገባበት ነገርም አይኖርም።

ባሉበት አንደበታቸው፣ ባለፈው ሳምንት በቁጥጥር ሥር የዋሉ ሰዎችን አስመልክቶ የሰጡት መግለጫ ላይ፥ ይደርስ የነበረውን የሰብዓዊ መብት ጥሰት የገለጹበትን መንገድ እናስታውሳለን። ቪዲዮውን እዚህ ይመልከቱ።

የበፊት ንግግራቸው መታወሱ ሲወራ፣ ወዲያውኑ ዋልታ የያኔውን ቪዲዮ ከድረ ገጹ ላይ ወዲያው ያነሳው ቢሆንም፣ ቀድመው ያወረዱት ሰዎች እየተቀባበሉት ተመልክተነዋል። (ዋልታስ ቪዲዮውን ማንሳቱ ምን ይባላል?)

እንግዲህ በደም የተጨማለቀ ስርዓትን በሀቀኝነት ማገልገል እና ሲደርስ የነበረውን ግፍ እና በደል ሁሉ፣ የሰብአዊ፣ የዴሞክራሲ እና የሕገመንግስት ሽፋን በመስጠት እንዳልነበሩ፥ አሁን ሌላው ላይ በሚናገሩት ነገር ህሊና ቢኖር ኖሮ አይሸመቅቅም ነበር ወይ?

ከላይም እንዳልኩት፥ ትናንት እንዲህ ተደርጎ ነበርና ዛሬ ዝም ይባል አይደለም። ቢያንስ ግን፥ ትናንት ተሳትፎ የነበራቸው፥ ከጋዜጠኛ እስከ ባለስልጣን፤ ከተራ አባል እስከ ፈላጭ ቆራጭ ድረስ፥ “ስላልተጋለጥን/ስለማንጋለጥ” በሚል ስሜት፥ ወይም በኖሩበት የአድርባይነት ስሜት፣ ነገሮችን ሲተርኩ፣ ፍጹም ከደሙ ንጹህ መስለው ለመታየት የሚያደርጉትን ነገር በልኩ ቢያደርጉት የሚል ነው። አሁንም ተጠያቂነት ድንበር አይኑረው!

እንግዲህ መመዘዝ የተጀመረው የሙስና እና የሰብዓዊ ጥቃት ክር የት ጋ እንደሚቆም በጉጉት እና በሌሎች በራሪ እንስሳዎች እናያለን! 😉

ዕድሜና ጤና ይስጠን እንጂ ከጊዜ ዳኝነት ማንም አያመልጥም!

ሰላም!

It will not be far…

The internet blackout and blockage of social networks in #Ethiopia is a blessing in disguise; and another big strategic mistake of the brutal government. It is a significant add-on to the mass protests, and tells the World once more again about the kind of government we have. As well, it has a good effect of letting the people focus on the effective and less costly interventions.
 
Our cyber activities were, somehow, keeping us aback from proper understanding of the extent that our freedom of speech is banned, and our potentials to get rid of it. Innermost, ‘being an active user of the internet’ might have created a humdrum feeling, and vapid feelings of ‘freedom fighter’ with every status update made and with every conversation held, while it hasn’t even kept us an inch closer to what is required and to our capacity.
 
If people are forced to logout facebook and other social networks, what the hell the tyrants are expecting them to do? They will login to the real world, and get organised in their communities to the fullest, so as to let brutality logout of the land for once and for all. The brutal regime is working hard to let that materialize, and organizing the people for a good cause of getting freedom.
 
Change is inevitable!, as “change will not come if we wait for some other person or some other time. We are the ones we have been waiting for. We are the change that we seek.” (Barack Obama) …and here we’re awake!, and we’ll stay united!
 
We have also learned that violence is a magic that multiplies defiant souls. When problems become devastating, solutions are promising. Now, the country has concerned and determined citizens more than ever. And speaking up for those who can’t is being a passion and it is being less confused with hard politics, and soon freedom will be a fashion for us to cherish and for our children to live in.
 
I am too positive that fighting for human rights and standing up with morale, in all fields, will be ordinary, not a bravery act for few to practice it and many to get astonished about.
 
It will not be far that they will pay the price; and amid, we will thank them for they are being on the power side of the powerless.
They have killed many, they have knocked on many houses. They have tried to close many doors and mouths, they have helped for many more to be opened. They distracted many alert and concerned citizens, they have alarmed on many dormant, ignorant, and natural ones. They have hammered many heads, they have awaken many neurones. They have given the earth a blood bath, they have called many to give blood for the nation to get a bath towards purity.
They raped a nation brutally, they have impregnated it breaking strong eggs with their inhuman sperms. They have killed, they have given birth to many. They didn’t know that throwing a seed means promising for it get rooted deep, and many of its kinds to come in fresh forms; as well, cutting the trunk is giving new branches a time of vegetating to trunks.
 
Through the blurs of our tears, we see many are joining in protesting the brutality, speaking up for those who can’t, and standing in solidarity with the victims. Now, concern will not be confused with politics, nor political awareness and activism will not be taken as a very wrong of the doers. Though a different kind of pain is inflicted in our hearts, eventually, knowing we all are mortals, we all know that it is a blessing in disguise.
They never loved us. They never loved to see us walking peacefully, to see us smiling, loving each one another, or having any undistracted day. Our peace is their mourn. Our holidays have been their peak times of terrifying us; our concerns and assemblies, their most terror. They were hate itself while we were celebrating Epiphany, Eid, Irreecha…even on the very secular great Ethiopian runs, they have been pains.
Demonstrations against violence of Saudi Arabia and Isis were among their public moments to show their sheer hatred for us. They have been distracting us with their guns, shackles, year gases, and physical and emotional tortures. Whether they saw us taking initiative to better community service plans, or they see us partake voluntarily, they never failed to see us with scorn. They never failed to prove us right that they have been consistent killers.
 
What has happened today is beyond our capacity to hold the pain, beyond what one can imagine, something that leaves one in shock even to properly cry about. I’m just acting weird; I can’t sit, nor I can stand properly…I can’t walk, nor loiter firm. I imagine how all you are feeling; it can’t be different, as our sufferings have been the same. They can’t hide it that it is a smart phone era that thousands have reported it with evidence. They couldn’t think, as we all have records in our minds. It is not about politics, but about humanity. It is not protesting, but speaking up against the devil itself.
 
But how many days shall we wait for?, how many nights to see us not being tortured to death? Is it the plan God? The beginning or the end? Revel, please. Egzio!
My heartfelt condolences to the innocent victims.
 
Death to bloody killers!
 

Governance and bullying steps – the Ethiopian (TPLF/EPRDF) way!

(Comment on Alula Solomon’s post)
 
1. Sing ‘developmental democracy’, and dance ‘federalism’ to cover the fascist and the racist in it.
 
2. Censor private medias, and force them to close if they won’t be submissive to the government. Persecution and imprisonment follow.
 
3. Spread consistently fabricated lies and propaganda, labeling every good initiative ‘terrorist and anti-development’ if it is not harmonious with the government’s mischievous and corrupt plans and deeds, terrify the people as if it is an angel and devil will takeover when it fall, using the state owned TV and Radios. Doing every possible thing, whatever it may cost: from the tax payer’s money to the lives of journalists, bloggers, activists and opposition party members, to close and/or slander other information doors.
 
4. Organize immoral thugs in the name of ministers, advisers, officers, and cadres; and gangs in the name of federal police.
 
5. Work evilly to brainwash education, culture, pride, and every good thing the people has accumulated out of penury; and scorn the oppressed majority.
 
6. Corrupt systems and resources, terrify steadily, call up the hard times they had as rebel group against the Derg regime, to implicitly induce that they deserve to oppress the people (bragging like the country is their colony), benefit selectively based on ethnic and political opinion in almost every other spot, and creating disparity between different nations of the country.
 
7. Gather, as their cadres, many optionless bootlickers that strive to support their daily subsistence with the money they get as an allowance for attendance of Kebele meetings. And use them for any public demonstrations called by the government, such as the late PM’s mass mourning ceremony.
 
8. Create feelings of second citizens and strangers in the people through their ruthless practice of nepotism, and merciless actions against the concerned citizens.
 
9. Violate the constitution. Ban peaceful demonstrations, and assemblies. Imprison and persecute concerned citizens. Murder the people for their peaceful protests.
 
10. Vandalize and destroy the people itself, not limited to it’s properties.
 
11. Spread hatred among the people that itself has worked hard to segregate in the name of federalism, to let them fight each one another to seek more ages of tyranny.
 
12. Disseminate fabricated stories about the protests, hijack the realities of the causalities in order to confuse as if there is attack against an ethnic group. Fabricate lies about damaged properties of one, while there are mass killings of the other by it’s own police officers.
 
13. Making low quality documentaries; while the people keep on suffering, and try to sign petitions in vain to international community, US government, EU, etc.
 
14. So much more.
 
#Ethiopia #StopKillingCivilians #OromoProtests #AmharaProtests

ፈርኦናዊነት

Hailemariam-Desalegnሰው ከመጽሐፍ ቢቀር ከእድሜው፣ ከእድሜው ቢቀር ከወዳጆቹ/ጎረቤቶቹ፣ ከነሱ ቢቀር አለትን ወደ አፈር በሚለውጠው ጊዜ፣ ከእርሱም ቢቀር ጨለማና ብርሃን ከሚፈራረቁበት የጠፈጥሮ ዑደት… እንዴት አይማርም?
 
በእኔ እምነት ይሄ ስርዓት እንኳን አሁንና ድሮም ያልፈረሰ፣ በከባድ ችግር ውስጥ እንኳን ገብቶ የማይፈርስ ስርዓት ነው። ስለዚህ በአለት ላይ የተመሰረተ ስርዓት አለን ብሎ ማመን ጠቃሚ ይሆናል። ….በዚህ ሂደት ውስጥ የተሳተፉ አካላትን ያለምህረት ህግ የማስከበር ስራችንን ማከናወን የሚገባን ይሆናል። መንግስት የህግ የበላይነትን ለማስከበር ሁሉንም አቅሙን ይጠቀማል። በእኔ በኩል ይህ የህግ የበላይነት እንዲከበር ለማድረግ ሁሉም የጸጥታ አካሎቻችን ህግ የበላይነትን እንዲያስከብሩ አዝዣለሁ።
ብሏል (ጠ/ሚ?) ኃይለማርያም ደሳለኝ
እንግዲህ ትዕዛዝ ማንበብ ነበርና ስልጣኑ’አለሁ’ ለማለት ጊዜ ተራው ደርሶት መሆኑ ነው ሕዝብ ለመፍጀት ትዕዛዝ ያስተላለፈው፡፡ ይሄ መቼም የሚረሳ ጉዳይ አይደለም!
 
ቃል በቃል ገልብጬው ደጋግሜ አነበብኩት። ደጋግሜ ነፈርኩኝ። የሰው ልጅ አእምሮ እንዴት በዚህ ደረጃ ሊደነዝዝ ይችላል? መቼስ ያደገ አገር ሰዎች ብንሆን እንዲህ ያለውን ሰው ሰብስበው ጥናት መከናወኑ አይቀርም ነበር።
 
“ፀጉራም ውሻ አለ ሲሉት ይሞታል” ነበር ተረቱ። “ፀጉራም ውሻ ሞቶም ሲታይ ጣረ ሞቱ ‘አለሁ’ ይላል” እንበለው ይሆን?!
.
.
ሰውዬው በሀይማኖተኛ ማሊያም እንደሚጫወት ትዝ ቢለን፥ ከመጽሐፍ ቅዱስ የፈርኦንን ታሪክ እናስታውሳለን….
 
“እግዚአብሔር እንደ ተናገረ፥ የፈርዖን ልብ ጸና፥ አልሰማቸውምም። እግዚአብሔርም ሙሴን አለው፦ የፈርዖን ልብ ደነደነ፥ ሕዝቡንም ለመልቀቅ እንቢ አለ።” (ኦሪት ዘጸአት 7፥ 13-14) “ግብፃውያንም፥ የፈርዖን ፈረሶችና ሰረገሎች ፈረሰኞቹም ሁሉ፥ እያሳደዱ በኋላቸው ወደ ባሕር መካከል ገቡ።” (ኦሪት ዘጸአት 14፥23)
 
“የሰው ልጅ ሆይ፥ ስለ ግብጽ ንጉሥ ስለ ፈርዖን ሙሾ አሙሽ፥ እንዲህም በለው። የአሕዛብን አንበሳ መስለህ ነበር፥ ነገር ግን እንደ ባሕር ዘንዶ ሆነሃል በወንዞችህም ወጥተሃል፥ ወኃውንም በእግርህ አደፍርሰሃል፥ ወንዞችህንም አሳድፈሃል።” (ትንቢተ ሕዝቅኤል 32፥2
 
“የመለስ መንፈስ ከኃይለማርያም ላይ ልቀቅ!” የምንልበት ጊዜ አልፏል። አሁን መንፈሱ ሙሉ ለሙሉ እንደተዋሃደው እያየን ነው። …እንግዲህ ሙሾ እያሞሸን ፍትህ ሲፈጸም የምናይበት ቀን ይመጣል! የሰው ልጅ ደም እንደው በከንቱ ፈሶ አይቀርም!
 
“ፈርዖንንና ሠራዊቱን በኤርትራ ባሕር የጣለ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና!” (መዝሙረ ዳዊት 136፥15)
 

ሀገሬን ከነኗሪዎቿ…

13925175_1450435844972892_1002811786806231956_nበስፖርቱም ሆነ በሌላው ጉዳይ አገሬን ከነኗሪዎቿ እንደ ሮቤል ኪሮስ ያስተዋወቀልኝ የለም። እንደሱ፥ በደልና ግፉን ሁሉ ባንድ ላይ ሸክፎ ለዓለም ያሳየልኝ የለም። ሙስናውን፣ ውጥንቅጡን፣ የወጣቱን ጉስቁልናና መገፋት፣ የስራ ማጣቱን፣ ሞያ ማቃለሉን፣ የሆድ ስፋቱን፣ የፖለቲካና የዘር መድልዎውን፣ የኑሮ ልዩነቱን (‘ሰላም ውሎ መግባት’ን ካለማወቅና ‘የጠሉትን የመቃወምን ዋጋ’ ካለመተመን፣ እስከ ‘የፈለጉትን ልዩ ነገር መሞከር’ መቻል ድረስ)… “መተዋወቅ” ላይ ኢትዮጵያ ከፍተኛ የሆነ መጭበርበር ደርሶባታል። ሀቀኛ ኗሪዎቿም ተበድለዋል።
 
ከትናንት በስቲያ ግን በሮቤል ቀፈት በኩል ሁሉም ነገር ታየ። በእርሱ ከአቅም በታች በሆነ ችሎታ ኦሎምፒክ ላይ መሳተፍ ሁሉም ነገር ፍጥጥ ብሎ ተነገረ። ሮቤልም አባቱም ያውቃሉ ብዙ ችሎታ እያላቸው ቤት የቀሩ ድንቅ ዋናተኞች እንዳሉ… ሌላ ሰው ተወክሎ ቢወዳደር የማሸነፍ እድል እንደነበረን… የሰውነት አቋሙን ዝርክርክነት (ፎቶው ላይ ወላ ተሰብስቦ ነው)… በምን መስፈርት እንደተመለመለና ባንዲራ ተሸካሚ እንደሆነ… እንዲህ ያሉ ትልልቅ ጉዳዮች ላይ አገርን ለመወከል ቀርቶ ለተራ የቀበሌ ሥራ፣ ሚኒማውን ማሟላት ማለት ዝምድና ወይም የፖለቲካ ትስስር መፍጠር ማለት እንደሆነ… ሌሎችም ብዙ ባለጊዜያት ያውቃሉ። ግን በቃ ሮቤል መሞከር የሚፈልገውን ነገር እንዲሞክርና “ለየት” ማለት እንዲችል፥ የአገሪቷን መስፈርት ያሟላል። እንደአባትና ልጅ ሊያሳፍር የሚገባ ጉዳይ ሳይቀር፥ እንደባለጊዜ ሲታይ አእምሮን ይደፍንና ያኮራል።
 
ከነኅሊና ከሆኑ ምን እውቀትና ጉጉት ቢሰንቁ፣ ሰተት አድርጎ የማያስገባውን የሥራና የሞያ ዓለም አሳየልኝ። በየትኛውም ዘርፍ፣ ሰው ምን ያህል ያሸበረቀ ሲቪ ቢኖረው፥ በልኩ የተሰራ ስራ ላይ ተወዳድሮ አገሩን ማገልገል ቀላል እንደማይሆንለት… በአንጻሩ፥ የሚፈለገውን ሞያዊ አቋም ያላሟላ ቦርጫም፥ ላዩ ላይ ተጣብቆ በሚያስጨንቀውም ሆነ፣ ሰፍቶት በሚወላለቅበት፥ የስራ ዓለም ላይ ገብቶ አገሩ ላይ መገልገልና ሕዝቧን መበደል መቻሉን አሳየልኝ። የራበውና ቤተሰብ ማስተዳደር ያለበት ሰው ህሊናውን ሸጦ፣ የማያምንበትን ሀሳብ እያራመደ ዳቦ ይገዛ ዘንድ የሚያስገድደውን የተጨማለቀ ሲስተም ፍንትው አደረገልኝ።
 
የተማሩና አገር ውስጥ መስራት ያልቻሉ ብዙ ሰዎች ለስደት ወጥተው በየበረሀው ቀርተዋል። የቀናቸውም በየሰው አገሩ ተበትነዋል። እንኳን የማይችሉትን ልዩ ነገር ለመሞከር ቀርቶ፣ የሚችሉትን ልዩ ነገር መስራት እንዳይችሉ በሀሳብ ልዩነታቸውና በፖለቲካ ተሳትፎአቸው የተነሳ ከየእስር ቤቱ ፍርግርግ ጀርባ የተወረወሩም ሞልተዋል። መንግስትን የሚቃወም መፈክር ያዛችሁ ተብለው ከዩኒቨርስቲ ትምህርት ገበታቸው ሳይቀር ተፈናቅለው ጥቃት የተፈጸመባቸውም አሉ። በየጎዳናው ለሰላማዊ ሰልፍ ወጥተው በግፍ ደማቸው የሚንዠቀዠቅ ወጣቶችም አይቆጠሩም። በአንጻሩ ደግሞ፥ የፖለቲካ ታማኝነትንና ዝምድናን ተገን አድርገው፥ ሳያንኳኩ፣ በተኙበት በሮች ተከፍተውላቸው ከቤት የሚጠሩ ቦርጫሞች አሉ። ይኼን ይኼን ሁሉ ሮቤል አሳየልኝ።
 
በአትሌቲክሱ እንኳን ብንመለከት፥ ብዙ ችሎታ ያላቸው ሰዎች ለሌላ አገር ባንዲራ እየሮጡ ነው። ከአገር ቤት የሚገፉት፥ እንዲህ እንደሮቤልና አባቱ ያሉ የኅሊና ቦርጫሞች እየተመረጡባቸው ነው። ይህኔ፥ እሱ ቀፈቱን ለዓለም ባሳየበት ቅጽበት ቅስማቸው ተሰብሮ የስደት በርን ያማተሩ ብዙ ዋናተኞች ይኖራሉ። በሌላውም ዘርፍ እንዲሁ። ….እንጦጦ ሄደሽ ብትወድቂ ብትነሺ፣ አገር እቅፉን በሚደንቅ ብቃት ብትሮጪ፥ አትሌቲክስ ማኅበሩ ዙሪያ ዘመድ ከሌለሽ ማንም አያይሽም። ብለሽ ብለሽ ሲመርሽ፥ እዚያ ለሚሮጡት ጀላቲና ቀዝቃዛ ውሀ በመሸጥ ራስሽን ለማስተዳደር ትሞክሪ ይሆናል። …ይኼን ይኼን ሁሉ ብዙ ሳያወራ አሳየልኝ።
 
ሮቤል አገራችንን በዋና ለመወከል ወጥቶ፥ በዋና ዋና ጉዳዮች ላይ ወክሎን ለዓለም አሳይቶልናል፣ እዚሁ እያለንም ለተጋረደብን ሰዎች ነገሮችን ገላልጦልናልና፥ ከእርሱ ይልቅ ፈልቅቆ ባሳየን አገር ላይ ዐይናችንን እንጣል።
 
የእርሱ ቦርጩን ማዝረክረክ የማሳፈሩን ያህል፣ የብዙ ቀልዶች መፈጠር ምክንያት ቢሆንም፥ እሱ እሱ እንዳያዘናጋንና መብታችንን ከመጠየቅ (ቢያንስ መበደላችንን በቅጡ ከመገንዘብ) እንዳያዘናጋን።
 
#Ethiopia #StopKillingCivilians

በአቅመቢስነት :-/

13507048_1604998063164033_3307705846976265661_nቀንቶት የሰው አገር ያየ ግን እንዴት ለአገሩ አይቀናም?? የሰውን አገር ስርዓት የተመለከተ ሰው እንዴት ለአገሩ ያንን አይመኝም?? የሰው አገርን የሰው ልጅ አከባበር ያስተዋለ ሰው ቀጥሎ እንዴት ሰውን ለማዋረድ (በዚያም ራሱን ለማዋረድ) ይፈቅዳል?? ባለስልጣናቱ በየስብሰባው፣ በየሽርሽሩ እና በየሰበብአስባቡ፣ በየተረተሩና ሸንተረሩ ሲንቀዋለሉ፥ እንዴት ነው… መንገዱን፣ ጽዳቱን፣ ስርዓቱን፣ ልምላሜውን፣ ጥጋቡን፣ ቅንነቱን፣ ሌላ ሌላ መልካሙን ሁሉ አገር ቤት ጭነው ስለመሄድ የማይቋምጡት??
 
ይገርማል! ሰው አገር ውስጥ ሰው ቢታመም፥ አስፈላጊውን ህክምና ከሰጡ በኋላ ነው ስለቢል የሚያወሩት፤ እንጂ ነፍስ ውጪ ግቢ የሚልን ሰው ህክምና አይነፍጉም። ዴሞክራሲያዊ ስርዓት በሰፈነባቸው አገራት፥ ፍትህ ይከበር ዘንድ፥ በወንጀል የሚፈለግ ሰው እንኳን እንደዋዛ በሞት ሲሰናበት ይበግናሉ። ቢችሉ አስታመው፣ አሻሽተው ነው ለፍትህ የሚያቀርቡት። (አሁን ለምሳሌ፥ ይሄን ሁሉ ነቀርሳ የተከሉት የቀድሞው ጠ/ሚ ሞት ልብ ተብሎ፣ በንጹህ አእምሮ ቢታሰብ እንዴት ያበግናል? እንዲሁ እንደጻድቅ ማሸለባቸው ሲታሰብ እንዴት ያንገበግባል? መቼስ ነፍስ የእግዚአብሔር ነውና ከሞት በኋላ አይፋረዱ ነገር!)
 
እነሱ ስለመንገድ እንጂ ስለተራማጅ ሰው ማውራት እርማቸው ነው። ስለህንጻ እንጂ ስለሰውነት መባዘን ሞታቸው ነው። …እንደው ህንጻና መንገዱንም በቅጡ በሰሩት እኮ! ሰው አገር ያለውን የመንገድ ስርዓት በቀዱት! ለፓርኪንግ (ለዚሁ ብቻ በታነጹ) ስንትና ስንት የተንጣለሉ ህንጻዎች ውስጥ ተሹሎክሉኮ መኪናውን ያቆመ ባለስልጣን፥ አገሩ ላይ ስለልማት ሲያወራ እንኳን፣ ጥራት እና ደረጃ እንኳን ህቅ አያደርገውም? “ልማት ልማት፣ እትት ብትት፣ ጸረ ልማት ኃይሎች…” ሲገርም! ሲያሳፍር!
 
“ኮንዶሚነም ተሰራ” ቢባል፥ ግማሹ በዝምድና እና በፖለቲካ ተሳትፎ ተደልድሎ የተረፈው፣ በስንትና ስንት ስለት እና ጾም ጸሎት በሚደርስ ዕጣ እንኳን፥ “ፈረሰ አልፈረሰ”፣ ሌት ተቀን በስጋት ነው። ደግሞ ሰው ስብሰባ ጠርቶ፣ ሰው አገር የታለፈ እና፣ ሌላ ሰው እንዲያነሳው በክብር የትም የሚጣል ጥሪት (ኩርሲ፣ ጠረጴዛ፣ መሶብ፣ ሶፋ፣ ብፌ፣ ቴሌቪዥን፣ አልጋ፣ መደርደሪያ፣ ሌላም ሌላም… ) ላይ ቤት መናድም አለ። የከርታታን ሰው፥ ተስፋንም፣ ጉጉትንም፣ ጥረትንም አብሮ መቅበር አለ። ከዚያ ሰላማዊን ሰው አውሬ ማድረግ! “ምን ልብላ” ብሎ ሥራ ሲፈልግ፥ ፈርዶበት አግኝቶት ለመንግስት ያፈነደደንና ሆዱን ለመጠቅጠቅ ሰፊውን ህዝብ በከንቱ ያስለቀሰ እና ያስቀመየን ምስኪን ፖሊስ ማስበላትና ደሙን በከንቱ ማፍሰስ! :-/
 
ከዚያ፥
 
“ሳሩን በልቶ ውሀውን ጠጥቶ የተኛውን በሬ፣
ጎትጉተው ጎትጉተው አደረጉት አውሬ” ይዘፈናል።
 
አንድን በሀሳብ የሚሞግት ተቃዋሚን ሰው፣ እሱንም በሀሰት ወንጅለው እንደማይገባው በግፍ ያንገላቱትን፣ ለህክምና እንዳይጓዝ በማገድ ማሰቃየት ክፋት እንጂ ሌላ ምን ይሆናል?? ከአገር ቢወጣ ምን እንዳይጎዳቸው ነው?? መቼስ አገር ውስጥ ሆኖ ከእንግዲህ ድኖ ለእነርሱ ሰው አይሆናቸው። ወጥቶ እንዳይቀር ሰጉ?? ምነው ይሄን ያህል፥ ሺህ ዓመት አይኖር! ሺህ ዓመት በድለው እና አሳቅቀው አይነግሱ! በየትኛውም አገር ታሪክ ከዚህ ቀደም ሲበድሉ የነበሩት ቀናቸው ሲደርስ ከቅጣት አለፉ??
 
ወዳጄ ሀብታሙ አያሌው የምታምነው አምላክ ይቅደምልህና በምህረቱ ይጎብኝህ! ቅድስት ማርያም ትዳብስህ! ልባቸውን ያራራልህና ወጣትነትህ ለቤተሰብህና ለህልምህ ይትረፍ!