የጉዞ ነገር…

images.jpgሁሉም የአፍሪካ አገራት ነዋሪዎች ወደኢትዮጵያ ለመግባት፣ በደረሱ ጊዜ ቪዛ ማግኘት የሚችሉበት አሠራር፣ ከኖቬምበር 10 ይጀምራል ተብሎ ነበር። (እንዴት ሆነ እንኳን “እንኳንስ ዘንቦብሽ እንዲሁም ጤዛ ነሽ” ይላሉ። የደህንነት ሁኔታው እንዲህ በሆነበት ጊዜ ጣጣው ብዙ ነው።
 
እሱን ባሉ በ20 ስንተኛ ቀኑ፥ አሁን ደግሞ ፓስፖርት ለማውጣት ቁም ስቅል ሆኗል ተብሏል። ወዳጆች ነገሩን ሲያወሩት ይኽን ያህል የተጋነነ ችግር አልመሰለኝም ነበር። ሰው እንዴት ፓስፖርት ለማውጣት መከራውን ያያል?
 
የሚሄድበት አገር ይጭነቀው እንጂ፣ እንዴት እና በምን ተለይቶ ይስተናገዳል?
 
ማን ነው አንቺ ቱሪስት ትመስያለሽ፣ አንቺ አትመስዪም ማለት የሚችለው?
 
በምንስ መስፈርት ነው?
 
ለምንስ እንደዚያ ይደረጋል?
 
በር ዘግቶ ስደት አስቀርተናል ለሚል ሪፖርት ነው?
 
ማንኛውም ሰው ከቦታ ቦታ የመንቀሳቀስ መብት አለው።
የሚሄድበት አገር አልቀበል ካላለው በስተቀርም፣ የፈለገበት ቦታ ሄዶ የመስራት እና የመኖር መብት አለው።
 
መብት የሆነውን ነፍገው፥ ምን ሸፍጥ እንዳሰቡ እንጃ… በጎን ለጎዳና ተዳዳሪዎች እና ለረጅም ጊዜ አዲስ አበባ ውስጥ ለኖሩ ሰዎች ጊዜያዊ መታወቂያ እንሰጣለን ይላሉ። ለምን አስፈለገ?
 
በዚህ በግርግር የቀበሌ ቤቶች ከድሃ ተነጥቀው ለባለጊዜ እየተሰጡ ነው ተብሎ በሚወራበት እና ምርጫና፣ ሕዝብ እና ቤት ቆጠራ በደረሰበት ጊዜ መታወቂያ መስጠቱ ለምን አስፈለገ?
 
መታወቂያው ቀርቶ ፓስፖርት ይሰጣቸውና እንደኢዮጵያዊ ይቆጠሩ።
 
#የጉድአገር